Site icon Dinknesh Ethiopia

የሽግግር መንግስት ማቛቛም ሂደት፣

Save Ethiopia Forum
በኢትዮጵያ ሊከሰቱ የሚችሉትን ቢሆኖች ካየን በኋላ አካታችና ዲሞክራሲያዊ 
የሆነ ስርዓት ለመፍጠር ምን ይደረግ በሚለው ላይ የሁሉም ትኩረትና አስተዋጽኦ 
ይጠይቃል። ኢትዮጵያን የማዳን መድረክ ለዚሁ መነሻ ሊሆን ይችላል ያለውን 
ፍኖተካርታ እንደሚከተለው ያቀርባል።

የሽግግር መንግስት የሚመሰረተው የለውጥ ሃይሉ አሸናፊ ሆኖ ሲወጣ ወይም መንግስትን በማስገደድ ወደ ድርድር ሲመጣ ነው የለውጥ ሃይሉ አካታችና አሳታፊ መሆን እንዳለበት ቀደም ሲል ተገልጿል። የለውጥ ሃይሉ ስንል ኢትዮጵያዊነትንና አንድነትን የተቀበሉ፣ ለፍትህና ለሰላም እንዲሁም ለዲሞክራሲ የሚታገሉትን የተለያዩ የታጠቁ ሃይሎችን፣ ክልልሎችን እና የፖለቲካ ድርጅቶችን ያካተተ ግንባር ማለት ነው። ይህ ግንባር በውስጡ ወይም በጋራ ከመንግስት ጋር በሚያደርገው የስልጣን ክፍፍል በሽግግር ጊዜ የህግ አስፈጻሚነትን (executive)ተግባር ይፈጽማል። የፍትህ አካሉ(judiciary) በነጻነት እንዲሰራ ይደረጋል። ፓርላማው ፈርሶ በሽግግር ወቅት የሚቋቋም ጊዚያዊ ህዝባዊ ሸንጎ ይኖራል። ህዝባዊ ሸንጎ በሽግግር ወቅት የሚያስፈልጉትን ህጎች ያጸድቃል። በህገመንግስቱ ለሽግግሩ እንቅፋት የሚሆኑትን አንቀጾች ያስተካክላል ወይም ያነሳል። ለመደበኛ ፓርላማ ምርጫን አስመልክቶ የሚያስፈልጉ ህጎችና አሰራሮችን ያወጣል። መደብኛ ፓርላማ ሲመረጥ ጊዚያዊ ህዝባዊ ሸንጎ ስራውን ያቆማል። የለውጥ ግንባሩም በፓርላማ ለሚመረጠው መንግስት ስራውን ይለቃል።

የለውጥ ግንባሩ የሽግግር ሸንጎ እስኪመሰረት ድረስ የመንግስት ስልጣኑን ይዞ እንደ ሞግዚት መንግስት ይሰራል። የሞግዝት መንግስት ስራና ሃልፊነት በዚሁ ሰነድ መጨርሻ ላይ ተገልጿል።

ግዚያዊ ህዝባዊ ሸንጎ ለማቋቋም አገራዊ መፍትሔ አፈላላጊ ግብረ ሃይል  ይቋቋማል። ይህ አካል የለውጥ ግንባሩ በሰየመው ኮሚቴ /አሰባሳቢ ኮሚቴ/ ይቋቋማል። የሚከተለውን ቅደም ተከተል ይዞ ይሂዳል፣

  1. አሰባሳቢ ኮሚቴ
  1. አገራዊ መፍትሔ አፈላላጊ ግብረ ሃይል

 

ሙሉ ሰነዱን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

Exit mobile version