abebayehu
Opinion

ውድ እናት አገራችን ከገጠማት ዘርፈ ብዙ ፈተና ለማሻገርና ሕልውናዋንም ለማስጠበቅ በልዩነት ሳይሆን በአንድነት በመቆም – አበባየሁ አሉላ

ዛሬን በድል መሻገር ለነገም ዲሞክራሲያዊ  መሠረቱን ማመቻቸት የሁሉም ባለድርሻ አካላት ድርብ ግዴታችን ሊሆን ይገባል!

አበባየሁ አሉላ
ዋሽንግተን ዲሲ

መግቢያ

እናት አገራችን ከፊት ለፊቷ አስከፊና አሳሳቢ አደጋዎች ተጋርጠውባታል! መላውን ዓለማችንን ያናጋው ሃብትና ስልጣኔ ረድፍ ላይ ያሉ አገራትን እየተፈታተነ ያለው የኮሮና ወረርሽኝ አደጋና በወገኖቻችን ሕይወት ላይ የደቀነው ስጋት እጅግ ከፍተኛ መሆኑ እውን ነው፤ ይህንን ተከትሎ የሚያስከትለው ማህበራዊ ቀውስና የምጣኔ ሀብት ውድመት ለደኃይቷ አገራችን እጅግ ከባድ ነው ፣ በተመሳሳይምን  ወኃችንን ለመጠቀም ባለመው የሕዳሴው ግድብ ግንባታ ሳቢያ በሉዓላዊነታችን ላይ ያጠላው የግብፅ ምኞት ፤  ጎሬቤት ሱዳንንም በመደለል ፣ አረብ ሊግንና አባል አገራትን በማስተባበር ፣ ወሮታ ፍለጋ አሜሪካንን ጨምሮ በአንድ ግንባር ማስተባበር መሞከርዋና በውጭ ግንኙነት ዘርፍ ያለ ዕረፍት በሃሰት ፕሮፓጋንዳ ኢትዬጵያ ላይ እየዘመቱ ነው! አልፈውም የመንግሥታቱ  ፀጥታውን ምክር ቤት ግንባታውን እንዲያስቆም መንቀሳቀሳቸው ምንስ ያክል ለጉዳዩ ትኩረት ስጥተው መስራታቸው ከፊት ለፊታችን የአጠላብን አደጋ ከባድ መሆኑን ጠቋሚ ነው ፣

እንደዚሁም የታሪክ አጋጣሚ ሆኖ  ሕገመንግሥቱና  ሕገመንግሥታዊ ቀውሱ ከአስከተለው መንገጫገጭ ጋር አገራችንን ለማሻገር ከምን ጊዜውም በላይ ሕዝባችን ፣ መንግሥት ፣ የፓለቲካ ድርጅቶችና በተለይም አንድነት ኃይሎች ፣ ሲብክ ማህበራትና ምሁራን ልዩነትን በማስወገድ በጋራ መቆም ታሪካዊ ግዴታችን ሊሆን ይገባል ፤

በዚህ ፁሑፌ እንዲሁ ሁኔታዎችን መተንተን ሳይሆን አገራችንና ሕዝባችን ትላንት ያለፈበትን ውጣ ውረድና የከፈለው መስዋዕትነት ያስገኘውን ውጤትና ያጣውን ማሳየት፣ ዛሬ የምንገኝበትን ነባራዊ ሁኔታውን የሚገመግም ፤ አፍጠው የሚጠብቁንን ችግሮች የሚዳስስና የመፍትሔ አማራጮችን በሚገባ ያስቀመጠ ይህንን ለመተግበር ኃላፊነት ያለባቸውንም አካላት ለይቶ ያስቀመጠ ፤ በአፈፃፀሙና አተገባበሩ ላይ መወሰድ ያለባቸውን ጥንቃቄዎች ለይቶ ያስቀመጠ  መጠነ ሰፊ ጉዳዬችን ያካተተ ስለሆነ በግርድፍ ሳይሆን ሙሉውን ተያያዥ ግንዛቤ እንድትወስድ በቅድሚያ አሳስባለሁ።

ውድ ኢትዬጵያዊያን!! ዛሬ የገጠመን ቀውስ በወገንተኝነትን ፣ በፓለቲካና የስልጣን ጥያቄ የሚፈታ ሳይሆን በጋራ ውይይትና መደማመጥ  አገራችን ለገጠማት ችግር እውነተኛ ፈውስ ሊሰጥ የሚችል ዘላቂ መፍትሔን መሻት የግድ ይሆናል ፤ ይህም እውን እንዲሆን በዳተኝነት የሚመስለንን በመወራወር  ሳይሆን እንደ አንድ የአገሩ ጉዳይ እንደሚያሳስበው ሁነኛ ዜጋ በጥሞና ተደማምጠን ያለወገንተኝነት በክብ ጠረጴዛ ዙርያ ሰብሰብ ብለን ነባራዊ ሁኔታውን ባገናዘበና መጪውንም ጊዜ ታሳቢ በአደረገ ጥናት ገምግመን ፣ በመረጃና ምክንያት ሃሳብ አዋጥተን የተሻለውንና ብዝኃኑ ላመነበት እራሳችንን አስገዝተን ለተግባራዊነቱ በእኩል መረባረብና መንቀሳቀስ ግድ ይሆናል! ይህም ሲባል እንዲሁ አንድን ወገን የማሞገስ ወይም የማጣጣል ጉዳይ  አይደለም ክርክሩ! መልካም ጅማሮዎች ተሳክተው በሕዝበኝነት እንዲቀጥሉም እንሻለን፣ ዛሬ እመሬት ላይ ከምናየው ነባራዊ ዕውነታ ተነሥተን መፍትሔ ፈልገንና ችግሩንም ፈትተን እውነተኛ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት በአገራችን እውን እንዲሆን እንዳለፉት ዘመናት መጪው ጊዜም አሁንም እንዳይቀድመንና ብሎም እንዳይደበዝዝብ ከወዲሁ አሻግረን በማየት የኢትዬጵያ ጉዳይ ያገባናል የሚሉ ወገኖች ሁሉ ድምፅ ይስማ ዘንድ ኢትዬጵያን የሚለው ኃይል ግዜ ሳይወስድ መላም መጠበቂያም ከወዲሁ  ሊያበጅለት ግድ ይላል።

የሕወኃት/ኢህአደግ አገዛዙ ሃያ ሰባት ዓመት ሕዝብን ቁም ስቅል ሲያሳይ እልፍ አዕላፍ ወገኖችን በበርካታ ማሰቃያ እስር ቤት ለዘመናት አጉሮ ግፍ ፈፅሟል! ሺዎች በዘረኝነት አለንጋ አገራቸውን ጥለው እንዲሰደድ አድርገዋል፣ብዙዎች ወዳቀድበት ሳይደርሱ የበረሃ አሸዋና ባሕር በልቶአቸዋል፣ ሌሎችም የሽብርተኞች ሲሳይ ሲሆኑ በሰናይ በረሃ ታግተው መሻገሪያ ገንዘብ የሌላቸው በቁማቸው የውስጥ አካላቸው ተሸንሽኖ ለሃብታሞች ሕይወት መቀጠል ሲሳይ መሆናቸውን በጀርመን ድምፅ ከስፍራው ላይ እማኝ አድርገው አሰምተውናል ።

እናት አገራችንን በጎጥ ከፍለው ዛሬ እንደ አሸን በፈላው የማንነት ጥያቄ ሳቢያ ወገን በእርስ በርስ ጥላቻ በተረጨው መርዝ እልፍ ዓዕላፍ ንፁኃን ዜጎች ሕይወት በከንቱ ጠፍቷል ፣ የንፁኃን ደም እንደጅረት ፈስዋል፣ በገጀራ የንፁኃን አንገት ተቀልቷል፣ እልፎች በድንጋይ ተወገረዋል ፣ ክቡር የሰው ልጅም ተዘቅዝቆ በራስ ወገን ሲሰቀል ለታሪክ አየን ፣ እናት በጠራራ ፀሐይ ልጅዋን የምታጠባበት ጡትዋ ተቆርጦም ሰማን ፣ የእናንት ቀዬ አይደለም ተብሎ ወላይታው አዋሳ በቁሙ በእሳት እንዲጋይ መደረጉንም በእማኝ ሰማን ፤ ከቤት ንብረታቸው ከቀያቸው ሚሊዬኖች አማራ ናቸሁ ወዘተ በሚል ተሰደድ፣ ዩኒበርሲቲዎች የዘር መጨፋጨፊያ ሆኑ ኳስ ሜዳዎችም በተመሳሳይ ፣ በጠራራ ፀሐይ መንግሥት አለ በሚባል አገር በቅርቡ ሴት ልጃገረድ ወጣቶች ታፍነው ተወሰድ ሰሚ አጥተው ተረሱ፣ የሕዝብ ሀብት በእሳት ጋየ ተዘረፈም ፣ ወንጀለኞች ተመሳጥረው በአንድ ጀምበር 17 ያክል ባንኮች በጠራራ ፀሐይ ዘረፉ ፤ ዛሬም ቢሆን በኦሮሚያ ክልል ቄሮ ባለንብረቶችን ይህንን ያክል ሺህ ብር ለነገ አዘጋጅ ብሎ ያዛልም ይነጥቃልም!!

ወገን! ይህ ሁሉ ሲሆን በርግጥ መንግሥት ሁሉም ሥፍራ አለን? የሚያስብል እንቆቅልሽ ነው ! ይህ ዛሬ በየቦታው የምናየው ዘር ተኮር ጥላቻ ፣ ግጭትና ቀውስ መድኃኒት ካልተገኘለት ቀጣይና የዚህ የሃያ ሰባቱ ዓመት ፅልመት ሥርዓት መሠረቱ አልተናደምና  እትዩጵያንና ኢትዬጵያዊነትን እንዳደበዘዘ ይቀጥላል።

በእዚህ ዓመታትን በወሰደውና ሺዎች ዋጋ በከፈሉት ሕዝባዊ እምቢተኝነት ሕዝብን የበላይ ሊያደርጉ የሚችሉ ብዙ መልካም አጋጣሚዎች አልፈውናል! ለምን? ህዝባዊ ቅንጅት፣ መርሕና መሪ ባለመኖሩ ይህ አስከፊ የሕወኃት/ኢህአደግ አገዛዝ አገርን ማስተዳደር ተስኖት እልፎች መስዋዕት ሆነው ከስረ መሠረቱ እስከነ ግሳንግሱ ሳይገርሰስ ቀጠለ።

በመሆኑም በግለሰቦች ሽግሽግ ሥርዓቱ ነፍስ ዘርቶ ቀጠለ! ከአብራኩ የወጡት ” የለውጥ ሃይል” በመባል ከነባራዊ የመንግሥታዊ ለውጥ ዕውነታው ውጭ ”  ጥገናዊ  ሂደቱን ” መሩት ሕዝባችን መስማት ይመኝ የነበረውን ቃል (ፈልቅቀው) አበሰሩለት ከጋመው የሕዝባዊ እምቢተኝነት የመተንፈስና የመረጋጋት ዕድልም ሰጡት!

” ኢትዬጵያዊነት ሱስ ነው” ብለው ተስፋን አሰንቀው ጮቤ አስረገጡን! ትንሽም ሳይቆዬ ወደ መንደራቸው ስንሸራተቱም ሰማን! እንደ ጎምም ድምፃቸው ለዘበ! ክህደት ወይንስ ማንነት? ለዚህም መፍትሔው ምንስ ይመጣ ይሆን ብሎ ነገን አሻግሮ ማየት ጎበዝ ግድ ይለናል ፤ የቀሩትም በዚህ ኢትዬጵያ በሚሏት አገር

” ስንኖር ኢትዬጵያዊ ስንሞት ኢትዬጵያ” ብለውን ስንትስ ዓመት የተጠማነውን ኢትዬጵያን ከፍ የሚደርግ ቃል ለሃያ ሰባት ዓመታት የተጠማንበት ቃል  አሰምተውን ልባችንን አሸፈቱት!! ባሉን ነገርም አብረውን ይዘልቃሉ አልን! ተከትለን ነጎድንም! ጎምቱ የተባሉ ሊሂቃንና ፓለቲከኞችም እዘለን! አሻግረንም አሉ! እሰዬው ስንል በበነጋታው አንዳንድ ፅንፈኞች ብዙ የተነገረላቸው አደባባይ ወጥተው …..

” ነፍጠኛውን እግር እግሩን ሰብረን ” ሲሉን ፣ በእውቁ ዩኒቨርሲቲ አዲሱን ትውልድ ይገራሉ የተባሉ ምሁራን መንደራቸው ወርደው ” ኦሮምኛ ካልተናገሩ አትሽጡም አትግዙም ” ብለው የዋሁን ሕዝብ ሲመርዙም ሰማን፣ ኢትዬጵያዊነትን ሲፀየፉ የነበሩ ባንዲራዋና ክብሯ በዓለም አደባባይ እንዳይሰማ የጣሩ በውጭው ዓለም ወሽመጣችንን የቆረጡትም እድሉን አግኝተው ለዓላማቸው መሳካት የኦሮሞን ወጣት ጓዳው ገብተው በግላጭ አገኙት በማንነት አሰከሩት!! አዲስ አበባም የእኛ ነው አሉን! አስደነገጡንም!

ማንን ከማንስ እንለይ መዘወሪያው በእነዚሁ እጅ ሆኖ ፈርጥመው ሕግን አስታከው አገሬን ብለው በዜዴ ሕልማቸውን ዕውን ያደርጉ ይሆን ብለን ኢትዬጵያን የምንል ኢትዬጵያ ትቀጥል ይሆን ብለን እንደትላንትም ተስፋም ስጋትንም ቢወራረስብን ትዝብትም ሊሆንብን ከቶውንም አይገባም ።

በዚህ ሁሉ ውጣ ውረድ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይና አመራራቸው ብዙ እጅግ አበራታችና ተስፋ ሰጪ በርካታ እርምጃዎች በመውሰዳቸው ኢትዬጵያዊያን ድጋፋችንን ሰጥተናል።

በውጭው ዓለም በስደት በኖርንበት ወቅት ኢትዬጵያውያን በአገራቸውና በወገናቸው ላይ ይደርስ በነበረው መራር የሰብአዊ መብት እረገጣ የአገሩን አገዛዝ በዓለም አደባባይ ወጥቶ በመቃወም ከአፍሪካ ግንባር ቀደሙን ሥፍራ ይይዛል ምናልባትምትም በዓለም አቀፍ ደረጃም ከቻይና በመለጠቅ ሁለተኛ እንሆናለን የሚል ግምት አለኝ!

ምንጭ፡ ዘ-ሐበሻ

ሙሉውን ለማንበብ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *