የኢትዮጵያውያንመረዳጃማህበርበኮሎኝናአካባቢው
Hilfsverein der Äthiopischen Gemeinschaft in Köln und Umgebung e.V
በታላቁ የዐባይ ሕዳሴ ግድብ፣ የመንግሥትንና የሕዝብን አቋም እንደግፋለን
በዓለም ውስጥ በርዝማኔ የአንደኝነቱን ደረጃየያዘው ነጭ ዐባይ፣ በተለይ ደግሞ 86% የሚሆነውን የውሃ አስተዋጽዖ የሚያደርገውና ለምአፈር በማጋዝ ለሱዳንና ግብፅ ታላቅ ሲሣይ ሆኖ እጅግ ሲጠቅማቸው የኖረው ጥቁር ዐባይመሆኑ እሙን ነው። ይህ አመንጪዋን ሀገር ኢትዮጵያን በመጉዳት የታችኞቹን የተፋሰሱ ሃገራት ሲያደልብየኖረው፣ በቅዱሱ መጽሐፍ ገነትን ከሚያጠጡ ፫ ወንዞች መካከል አንደኛው
መሆኑ የሚነገርለት ዐባይ፣ ፈለገ ግዮን በመባልምይታወቃል።
በፈርዖኖች ዘመን የጥንት ግብፃውያን ጥቁር ዐባይ የሚመነጭባትን ኢትዮጵያን «የፈጣሪ ማደሪያ» እያሉ ነበረ የሚያወሷት። የሕይወት መሠረትየሆነው ውሃ በገፍ እየመነጨ ግብፅን በመታደጉ ጥንታውያኑ ኑዋሪዎቿ፣ የውሃው ምንጭ መገኛ የሆነችውን ሀገር «የፈጣሪ ማደሪያ» ብለው መጥራታቸው፣ ገለታቢሶች እንዳልነበሩ ይጠቁማል ማለትይቻላል። ይሁንና በዓለም ታሪክ ውስጥ ከ 19 ኛውክፍለ ዘመን ወዲህ ይሉኝታን ያጠፋ ሁኔታ ሳይከሰት አልቀረም። የአፍሪቃ ክፍለ ዓለም በአውሮፓውያን ቅኝገዥዎች ሥር የወደቀበት ያ ክፉ ዘመን፣ ጉልበት እንጂ ፍትሕ እንደማይበጅ
የተሣሣተ ምልከታን አስጨብጦ ይመስላል ያለፈው። የአፍሪቃ አህጉር(አገሮች) ከቅኝ አገዛዝ ነጻከወጡ በኋላም ቢሆን፣ በአንዳንድየክፍለ ዓለሙ ሃገራት ዘንድ የቀድሞ ቅኝ ገዥዎች መርሕ፣ እንደ ትክክለኛ አሠራርም ሆነ ደንብ የተወሰደ ይመስላል።
በዘመናችን፣ ይህንአመለካከት ከሚያንጸባርቁ ሃገራት መካከል አንዷ፣ እ.ጎ.አ. የካቲት28 ቀን1922 ዓ ም ከብሪታንያ ቅኝ አገዛዝ ነጻየወጣችው ግብፅናት።ግብፅ፣ በ
1929 ዓ ም ከብሪታንያ ጋር፣ በ1959 ደግሞ ከሱዳን ጋር የጥቁር ዐባይን ውሃ መንጪዋን
ኢትዮጵያንም ሆነ የነጭ ዐባይንተፋሰስ አገሮች ሳታነጋግር፣ ውሃው የሁለቱ አገሮች ብቻ እንደሆነ አስመስለው ውልመፈራረማቸውየሚታወስነው።
ኢትዮጵያ፣ ጥቁር ዐባይ እርሷን እየጎዳ የታችኛውን ተፋሰስ አገሮች ግን የቱን ያህል እንደጠቀማቸው ብታውቅም፣ ዐቅም በማጣት ለብዙ ዘመናትየበይተመልካች ሆና መቆየቷ የማይታበል ሐቅ ነው።
ሆኖም፣ ጊዜው ሲደርስ፣ የሕዝቧንም ቁጥር እጅግመናር አገናዝባ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨት፣ ልማቷን ለማፋጣን፣ ድህነትን በሰፊውለመቅረፍ ዋና መፍትሔ አድርጋ የተመካችው በሕዳሴው ግድብ ላይ ሆኗል።ከአሥር ዓመትገደማ በፊት መገንባት የጀመረው ግድብ አሁን በመገባደድ ላይሲሆን የውሃ ሙሌቱ በሀምሌ ወር ይጀመራል ተብሎ በኢትዮጵያውያን ዘንድ በታላቅ ጉጉት በመጠበቅ ላይነው።
ኢትዮጵያ፣ ከግዛቷ የሚመነጨውን ውሃ ለልማት ማዋል የተፈጥሮ መብቷ ቢሆንም፣ የታችኛው የዐባይ ወንዝ ተፋሰስ ሃገራት እንዲያውቁት፣ ሁሉም ፍትሓዊ ተጠቃሚዎች እንዲሆኑ፣ ከ፭ ዓመት በፊት በጋራ፣ በሱዳን መዲና በካርቱም፣ የሦስቱ ሃገራት፣ማለትም የኢትዮጵያ፣ የሱዳንና የግብፅ መሪዎች ታሪካዊ የተባለለትን፣መሠረታዊ የፍትሐዊ ተጠቃሚነት የመርሕ ሰነድ መፈረማቸው የሚታወስ ነው።
ይሁን እንጂግብፅ፣ ከኢትዮጵያና ሱዳን ባፈነገጠ መልኩ የሕዳሴው ግድብ ሥራ እንዲስተጓጎል ውሃውም፣ ያለኔ ወይም ያለ ሦስታችን ፈቃድና ስምምነትእንዳይሞላ በማለት የዲፕሎማቲክ ዘመቻ ስታጧጡፍ ከመክረሟም በላይ፣ ወታደራዊ ዛቻ ጭምር እስከማሰማት መድረሷየሚታበል አይደለም።
ግብፅ፣ የዐረብ መንግሥታትን ማሕበር ብቻ ሳይሆን፣ የዩናይትድ ስቴትስ አስተዳደር፣ እንዲሁም የታወቁ «ዓለም አቀፍ» የገንዘብ ተቋማት በኢትዮጵያላይ ጫናእንዲያሳርፉ ያደረገችው ውትወታ የመተግበሩ ምልክት እየታዬነው። በዓለም ዙሪያ፣ የገለልተኛ መንግሥታት ብቻ ሳይሆን፣ የአፍሪቃ ሕብረትና የዐባይ ተፋሰስ ሃገራት ፍትሓዊ የአቋምጽናትየሚጠበቅቢሆንም፣ውዝግቡን በድል አድራጊነት ለመወጣት፣ ከኢትዮጵያ በኩልየሚፈለገው፣ ሉዓላዊነትን አስከብሮ በነጻነት ጽኑ አቋምንና ብልሃትን የሙጥኝ ብሎ የሚንቅሳቀስ የመንግሥት አመራርና የሕዝብ አንድነት ነው። ይህደግሞበሀገር ወስጥና በውጭ ሀገራትየሚኖሩትን ኢትዮጵያውያን ዜጎችንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን ሁሉ