tplf
News

ከጥቅምት 5/2012 ጀምሮ በራያ ሕወሓት ለጦርነት የሚያደርገውን ዝግጅት አጠናክሯል

ህብር ረዲኦ እንደዘገበው በዛሬው ዕለት ጥቅምት 5/2012 በራያ ሕወሓት ለጦርነት የሚያደርገውን ዝግጅት አጠናክሯል።ጥይት፣የወታደር ዩኒፎርም፣ቃሬዛ እና አካፋ ለታጣቂዎች እያከፋፈለ ነው።
የራያ ማንነት አስመላሽ ኮሚቴ የሕዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ ደጀኔ አሰፋ የሕወሓትን የጦርነት ዝግጅት የፌደራል መንግሥት እና አዴፓ ሊያውቁት ይገባል ሲል መረጃውን ይፋ አድርጉዋል።

ሰሞኑን ለአንድ ሳምንት ስብሰባ ላይ የቆየው ሕወሓት ትላንት ባወጣው መግለጫ የኢህአዴግን ውህደት ተቃውሞ፣ሕዝቡ ለመራራ ትግል ይዘጋጅ ሲል ጥሪ ማድረጉ አይዘነጋም። ተከታዩን ጥሪ ያንብቡት ሼር ያድርጉት

ጥብቅ መልዕክት ለፌደራል መንግስት እና ለአዴፓ
————
ዛሬ ጥቅምት 5 ቀን በዚህ ሰዓት ለራያ ሚሊሻዎች ስምንት ስምንት ካርታ ጥይት (240 ጥይቶች) ፣ የሚሊተሪ መለዮ ፣ አስከሬን እና ቁስለኛ ማንሻ ቃሬዛ ፣ አካፋ ፣ ዶማ ወዘተ በአላማጣ አስተዳደር ፅ/ቤት ፊት ለፊት እየሰጧቸው ይገኛል። የፌደራሉ መንግስት እና አዴፓ ለእንደዚህ አይነት የትንኮሳ እንቅሰቃሴዎች በቂ ትኩረት ሊሰጥ ይገባል። የራያ ሚሊሻ መሳሪያህን እና ጥይትህን አጥብቀህ ያዝ። ምክራችን እውን የሚሆንበት ጊዜ ቅርብ ነው!!

Source: ZeHabesha

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *