ሳህለወርቅ
News

“ቀይ መስመር ተጥሷል…!!!” ፕ/ት ሳህለወርቅ ዘውዴ

ሰሞኑን በአዲስ አበባ እና በተለያዩ የኦሮሚያ ከተሞች ውስጥ በአብዛኛው ዘር እና ሀይማኖትን ኢላማን ያደረገው እና ለበርካታ ዜጎችን ህይወት እንዲቀጥፍ ምክንያት የሆነው ጭፍጨፋ “ቀይ መስመሩን ያለፈ ነው” ሲሉ ፕ/ት ሳህለወርቅ ዘውዴ ድርጊቱን በጽኑ አወገዙ።

ፕ/ት ሳህለወርቅ በወዳጆች መገናኛ መረብ የቲውተር ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት ጽሑፍ” ዘር እና ሀይማኖት ለፖለቲካ ጥቅም እንዲውሉ ሲደረግ፣ንጹሀን እና ሰላማዊ ዜጎቻችን በአሳቃቂ ሁኔታ ሲገደሉ፣ሲፈናቀሉ እና ሲሰደዱ ስናይ ስሜትን ለመግለጽ ቃላት ያጥራል፣ለቅሶ ድንጋጤ እና ስጋት የብዙዎችን በርን አንኳኩቷል።ሀዘናቸው ሀዘኔ ነው”በማለት እጅግ አሳዛኝ እና አሳፋሪ በሆነው ድርጊት መቆጨታቸውን በግላጭ ተናግረዋል።
ወደ ፕ/ትነት ስልጣን ከመምጣታቸው በፊት ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን በመወከል ከሰላሳ አመት በላይ በዲፕሎማትነት ያገለገሉት ፕ/ት ሳህለወርቅ የትዊተር መልክታቸውን ሲቀጥሉ”ለሀገር እና ለህዝብ ጥቅም ሲባል ልናሰምረው እና ልናከብረው የሚገባው ቀይ መስመር ተጥሷል፣ሀገራችን ካንዣበበባት ክፉ አደጋ ለማዳን ሁላችንም ሚና አለን፣የሚመለከታቸው ሁሉ የየበኩላቸውን ሀላፊነትን መጫወት አለባቸው፣ቀዩ መስመር መጣስ የለበትም እንበል”በማለት ስርአት አልበኞችን መዋጋት ለአንድ ተቋም ብቻ የሚሰጥ ሳይሆን በሀገሬ ጉዳይ ያገባኛል የሚል ሰላም ወዳድ ዜጋ ሁሉ እርብርቦሽ እንዲያደርግ ተቃውሞ አዘል ጥሪ አቅርበዋል።

እንደ የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት ኮሚሽን መግለጫ ከሆነ በሰሞኑ ግጭት ከሰማኒያ በላይ ዜጎች ህይወታቸውን ያጡ ሲሆን የአሟሟታቸውንም ሁኔታ በተመለከት ኮሚሽኑ እንደታዘበው አስር የሚሆኑት ብቻ በጥይት ተመትተው የሞቱ ሲሆን የተቀሩት በድንጋይ ተወግረው፣በስለት ተወግተው እና በዱላ ተጨፍጭፈው እንዲሞቱ መደረጉን የኬሚሽኑ መግለጫ ይገልጻል።
ከዚህ በመቀጠልም ከወንጀሉ ጋር በቀጥተኛ ሆነ በተዘዋዋሪ ግንኙነት ያላቸው በሙሉ በህግ እንዲጠየቁ አሳስቧል።
የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን በበኩሉ ከስሞኑ እልቂት ጋር የተጠረጠሩ ወደ ሶስት መቶ ሀምሳ ዘጠኝ ግለሰቦችን በቁጥርጥር ማዋሉን አስታውቋል።

(በታምሩ ገዳ/ህብር ራዲዮ)

Source: ZeHabesha

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *