– አለማየሁ አበበ
Opinion

የሰሞኑ ጥቃት! – አለማየሁ አበበ

የጥላቻ ንግግር በህግ የሚያስጠይቅ ከሆነ በቅድሚያ ብዙ የኦሮሚያ ቁንጮ የመንግስት ባለስልጣናትና ካድሬዎች ላይ ጉድ ሊፈላ ይሆን ?

ይህን የምለው በግምትና በጥርጣሬ ሳይሆን ቢያንስ ባለፈው አንድ አመት በተለያዩ ኢቨንቶች ; ስብሰባዎችና የመሣሠሉት ጊዜያት በአፋን ኦሮሞ ለታዳሚዎቻቸው በሚያደርጉት ንግግር ; በማህበራዊ ሚዲያ በሚፅፉት ፅሁፍ : ምናልባትም ለመወደድና ለኦሮሞ ፍፁም ወገንተኞች ናቸው እንዲባሉ የሚጠቀሙበት ቃላቶችና አባባሎች በግልፅ ጥላቻን የሚያንፀባርቁ ናቸው ። ሕጉ ወደኋላ ላለፈው የሚሠራ ቢሆን ኖሮ መረጃውና ማስረጃው ሺህ ነበር ።

በጣም የሚገርመው ደግሞ እነኚህ ተናጋሪዎች ወይም ፀሀፊዎች እንዲያ ሲናገሩና ሲፅፉ ከኦሮሞ ውጪ ሌላ ማንም አፋን ኦሮሞ መናገር : መስማት : መፃፍና ማንበብ የሚችል ያለ አይመስላቸውም፨ ሁሉም ጨርሶ የማይችል ይመስላቸዋል እንዴ ? ለአብነት ያህል እንደምሣሌ የሚጠቀሙባቸው ቃላቶች ብንጠቅስ የኦሮሞ ሕዝብ ኦሮሞ ያልሆነን ሌላ ኢትዮጵያዊ በኦሮሞ ዘንድ እንደ ጠላት : እንደ ክፉ ባላንጣ እንዲታይ : እንዲጠረጠርና ጭራሽ ለኦሮሞ ጭቆና ;ምዝበራና ሰቆቃ ምክንያት እንደሆነ ተደርጎ በኦሮሞዎች ጭንቅላት እንዲቀረፅ ሆን ብለው የሚናገሩና የሚፅፉ ይመስላል ።

ምሣሌ ብንጠቅስ ዘወትር በተደጋጋሚ ከንግግራቸውና ከፅሁፋቸው የማይጠፋው “ዲኒ ” “ዲኒ ኬኛ” የሚለው ኦሮምኛ የአማርኛ ትርጉሙ “ጠላት ” ጠላቶቻችን ” የሚለው መቼም ጣሊያንን ወይም እንግሊዞችን ነው የሚሉት አትሉኝም ። ሌላው ዘወትር ከአፋቸው የማይጠፋው “ጀሪ ” የሚለው ኦሮምኛ ሲሆን የአማርኛ ትርጉሙም ” ሰዎቹ (non-oromos” ወይም እንደ አረፍተ ነገሩ አገባብ “የኛ ያልሆኑት ሠዎች” ማለት ሲሆን ኦሮሞ ያልሆኑ ኢትዮጵያኖች ለኦሮሞ ወገንተኛ አንደማይሆኑ የሚፈረጁበትና ለኦሮሞ ጥሩ አመለካከት ያሌላቸው ናቸው የሚል እንድምታ ያለው ነው ። ሌላው በጣም የተለመደውና የሚያሣዝነው ቃል “አለጋ” የሚለው ሲሆን ትርጉሙ “ባዕድ” ማለት ነው ።

በንግግራቸውና ፅሁፋቸው አገባብ ደግሞ ኦሮሞ ያልሆነ ሠው ወይም ስብስብ ወይም ቡድን ሁሉ ለኦሮሞ እንደ ባዕድ የሚቆጠርና የሚፈረጅ የጥላቻ ስሜት ያዘለ ነው ። በጣም ያሣዝናል ። ኦሮሞ በባህሉ አቃፊና ሰው ከኦሮሞ ባይወለድም በጉዲፈቻም ሆነ በሌሎች የባህሉ ትሩፋቶች ኦሮማይዝ የሚያደርግ ነው እየተባለ ጊዜ አገኘን የሚሉ ባለስልጣናትና ካድሬዎች ይህን የጥላቻ መርዝ ሲረጩ ምን ይባላል ? ከፊሉ በኦሮምኛ የተናገሩት ነገር ተተርጉሞ ሲወጣባቸው ይቅርታ እንደመጠየቅ ስም ለማጥፋት ነው ገለመሌ እያሉ ይከራከራሉ ።

እስቲ ይህን የኔን ትዝብት ኦሮምኛ የምትችሉ ሰዎች ሌሎችን የለየላቸውን ሚዲያና አክቲቪስቶችን ብቻ ሳይሆን ባለስልጣናትና ካድሬዎችን በኦሮምኛ ሲናገሩ ተከታተሉና አዳምጧቸው ወይም በማህበራዊ ድረገፅ ላይ የኦሮምኛ ፅሁፋቸውን አንብቡና ፍረዱ ።

የጥላቻ ንግግርና ፅሁፍ ህጉ ያለምንም አድሎ የሚፈፀም ከሆነ የመጀመሪያ ሰለባዎቹ ማን እንደሚሆኑ ለማየት ያብቃን ።ሰሞኑን እየደረሰ ያለው ጥቃት እኔ ላይ እንደደረሰ ነው የምቆጥረው ለሞቱት ነብስ ይማር ለቤተሰቦቻቸው መጽናናትን እመኛለሁ።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *