*ከኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ – ኢሕአፓ የተሰጠ መግለጫ* በአሁኑ ወቅት በሀገራችን ኢትዮጵያ ዜጎች በህግ ጥላ ስር የመጠበቅ መብታቸው ተጥሶ፣ ከየቤታቸው በፀጥታ አካላት ከተወሰዱ በኋላ ያሉበት ሳይታወቅ ደብዛቸው የመጥፋቱ አሳሳቢ ክስተት ቀጥሏል። በተለይም ከአንድ አመት በፊት ከአዲስ አበባ ከተማ ተይዘው የተወሰዱ ወጣቶች እስካሁን ድረስ ያሉበት አድራሻና የደህንነት ሁኔታ አለመታወቁ ፓርቲያችንን እና መላውን የኢትዮጵያ ሕዝብ እጅግ አሳስቧል። Read more
Press Release
“Never Again” has become an empty slogan. A statement from Amhara Unity for Resistance (Amhara Unity)
“Never Again” has become an empty slogan. While the world commemorates past genocide, it’s actively ignoring a living one, #AmharaGenocide A statement from Amhara Unity for Resistance (Amhara Unity) (February 13, 2026) It has been three years since Abiy Ahmed declared war on the Amhara people. Since January 26, 2026, the Abiy regime has intensified Read more
Statement to International Media Covering the AU Summit in Addis Ababa
As you report from Ethiopia during the African Union Heads of State meeting, we urge you to uphold the core principles of journalism: truth‑seeking, independence, and accountability to the public. While diplomatic events in Addis Ababa draw global attention, communities in Amhara, Oromia, Tigray, and other regions continue to experience violence, including documented drone strikes Read more
በ7ኛው ዙር ምርጫ ተሳትፎየን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ
ለተከበራችሁ የባሕር ዳር ከተማ ነዋሪዎች፣ ለመላው የአማራ ሕዝብ እና ለኢትዮጵያውያን ወገኖቼ በሙሉ፦ ባለፉት ዓመታት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውስጥ በኩሩው የባሕር ዳር ከተማ ሕዝብ ተመርጨ፣ እናንተን ወክዬ፣ ለሕዝባችን ሀቀኛ ድምፅ በመሆን ለማገልገል በመቻሌ ታላቅ ክብርና ኩራት ይሰማኛል። በዚህ ጉዞዬ ላሳያችሁኝ ያልተቆጠበ ድጋፍ፣ ፍቅር፣ አክብሮት እና ጽኑ እምነት ከልብ የመነጨ ምስጋናዬን አቀርባለሁ። በአሁኑ ወቅት ለ7ኛው ዙር Read more
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ መመስረቱን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ
የኢትዮጵያ ትብብር ንቅናቄ የፋኖ ኃይሎች ጥር 09፣ 2018 ዓ.ም. የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ በሚል ስያሜ ውህደት መፍጠራቸውን በማበሰራቸው የተሰማውን ጥልቅ ደስታ ይገልጻል። የአማራ ሕዝብ በጠባብ ብሄረተኞች አገዛዝና አምባገነናዊ ስርዓተ መንግስት ላለፉት 30 ዓመታት ከፍተኛ ግፍና ሰቆቃ የደረሰበት መሆኑን አይተናል። እያየንም ነው። አማራ በማንነቱ ሲገደል፣ ሲፈናቀል፣ ሲሳደድ እያየን ነው። ይባስ ብሎ አሁን ያለው የአብይ አህመድ Read more
ከጦርነት የተረፉ ንጹሀን በረሀብ እየተገረፉ መሆኑ ትልቅ የሰብዓዊነት ልሽቀት ነው!
ከጦርነት የተረፉ ንጹሀን በረሀብ እየተገረፉ መሆኑ ትልቅ የሰብዓዊነት ልሽቀት ነው! * በሕፃፅ የመጠለያ ካምፕ የተከሰተውን ረሀብ አስመልክቶ ከኢሕአፓ የተሰጠ መግለጫ* ላለፉት አመታት በከፍተኛ ጦርነት ሲሰቃይ የቆየው የትግራይ ሕዝብ አሁንም ፖለቲካ ወለድ በሆነ ምክንያት በከፍተኛ ስጋት ውስጥ መሆኑን ፓርቲያችን ተመልክቷል። ባልተገባ መንገድ በአገር ውስጥ እና በውጭ ሀይሎች ጦርነት ላይ የቆየው የትግራይ ሕዝብ ለምን ከጥይት አመለጥክ? በሚመስል መልኩ በሰው ሰራሽ ርሀብ ሳይታይ እና ሳይምሰማለት እየተገርፈ ይገኛል። Read more
በነፃነት የመሰብሰብን መብት በማፈን የሚፀና ሥርዓት አይኖርም፤ ብልጽግናም ራቁቱን ቀርቷል
ህዳር 26፣ 2018 (ዲሰምበር 5፣2025) ኢህአፓ ህጋዊና መሰረታዊ መብቱን በመጠቀምና ህጋዊ መንገድን በመከተል አዲስ አበባ ላይ ለህዳር 27፣ 2018 (December6, 2025) የህዝብ ስብሰባ ለማድረግ ዝግጅቱን ሁሉ አጠናቆ እንደነበር በሰፊው ይታወቃል። የአዲስ አበባ ወታትም ይህን ሰብሰባ ለማታደም በከፍተና ጉኡት ሲጠብቅ እንደነበር የተለያዩ መረጃዎች አሳይተዋል፡፡ ሆኖም ግን በመጨረሻው ሰዓት ላይ ብልፅግና ስብሰባው እንዳይካሄድ በቀጥታም ይሁን በተዘውዋዋሪ መንገድ የተለመደዉን የዲሞክራሲ ሆነ Read more
TENSIONS IN THE HORN OF AFRICA ESCALATE AMID ONGOING CONFLICT IN ETHIOPIA
The security and human rights situation in Ethiopia, and the broader Horn of Africa, has sharply deteriorated amid recurrent and escalating conflicts, placing already vulnerable populations at increased risk of grave abuses. This deterioration is starkly evident in the Amhara region, where conflict between the Fano, an ethnic Amhara militia, and the federal government has intensified Read more
እንዳያማህ ጥራው፤ እንዳይበላ ግፋው› አዲሱ የብልጽግና የአፈና ስልት!
የተፈራው ደረሰ!! ያሳዝናል!! *ከኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) የተሰጠ መግለጫ* ኢሕአፓ የኢትዮጵያ ችግሮች የሚፈቱት በራሱ በኢትዮጵያ ህዝብ የተባበረ ሰላማዊ ትግል ነው ብሎ በጽኑ ያምናል። ፓርቲያችን ከቆመለትና ለመብቱና ጥቅሞቹ መጠበቅም ከሚታገልለት ህዝብ ጋር ለመወያየት ከአዲስ አበባ ነዋሪዎች ጋር ቅዳሜ ህዳር 27 ቀን 2018 ዓ.ም በተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች ታሪክ ከረጅም አመታት በኋላ የመጀመሪያ የሆነውን ህዝባዊ ስብሰባ Read more
November 30, 2025 ስለ ኢትዮጵያውያን ትብብር ንቅናቄ ጠቅላላ ዓመታዊ ጉባኤ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ! የኢትዮጵያውያን ትብብር ንቅናቄ አጠቃላይ ዓመታዊ የዙም ጉባኤውን ከ70 በላይ የሚሆኑ እንግዶች በማስተናገድ ቅዳሜ ኅዳር ፲፫ ቀን ፪፼፲፰፤ (November 22, 2025) ተካሂዶ፣ በጣም በተሳካ መንገድ ተከናውኗል። ጠቅላላ ጉባኤው ከመጀመሩ በፊት በትብብሩ ሊቀ መንበር ጋባዥነት፣ በምስራቅ አርሲ በኦርቶዶክስውያን ላይ የሚካሄደውን ግድያ በማስታወስ፣ በአማራ ክልል በድሮን እየተጨፈጨፈ Read more
የኢትዮጵያ ሕዝብ ታላቅና አኩሪ መስዋዕትነት ከፍሎ ያቆያት ሀገሩን ዛሬም ከጥፋት ይታደጋት!! ከተባበረ ይችላልም!!!
ይህ የኢሕአፓ የወቅቱ የትግል ጥሪ ነው! ሀገር የዜጎቿ እጅ ስራ ናት። የሀገር ህይወቷም፣ ልማቷም፣ ዕድገቷም፣ ሠላሟም፣ውበቷም የሚገኘው ከሕዝቧና በሕዝቧ ጥረት ነው። ያለሕዝቧ ሁለንተናዊ በይነግብር ሀገር ምደረበዳ ነች። ኢትዮጵያን እልፍ አዕላፍ ዜጎቿ ደማቸውን አጉርፈው ውቅያኖስን አቅልመው፣ አጥንታቸውን መርከብ አድርገው፣ ገጣጥመው፣ አያሌ ማዕበሎችንም ተቋቁመው፣ ቀዝፈው፣ ተሻግረው፣ ከትውልድ ወደ ትውልድ አስተላልፈዋታል። በቀደሙት ልጆችዋ አርቆ አሳቢነት፣ ቁርጠኝነት፣ ሁኔታዎች ግድ Read more
የአረመኔው የአብይ አህመድ ፋሽስት ሰራዊት በወጣት አርበኛ ሴቶቻችን ላይ የፈጸመውን የጭካኔ ጥግ መላው ዓለም ሊያውቀውና ሊያወግዘው ይገባል!!!
የአረመኔው የአብይ አህመድ ፋሽስት ሰራዊት በወጣት አርበኛ ሴቶቻችን ላይ የፈጸመውን የጭካኔ ጥግ መላው ዓለም ሊያውቀውና ሊያወግዘው ይገባል!!! የፋኖ ሰራዊት የጠላት ወታደር ቁስለኛ ምርኮኛ በቅድሚያ ህክምና እንዲያገኝ ሲያደርጉ፣ ሌላውም ምርኮኛ ደግሞ በምህረት ወደ ቤተሰቦቹ እንዲሄዱ ያደርጋሉ። ምርኮኞች ቁጥራቸው በርከት ሲልም ዓለም አቀፍ ቀይ መስቀልን በመጠየቅ እንዲረከባቸው ያደርጋሉ። የታወቀውን የዓለም አቀፍ ምርኮኛ አያያዝን ህግ ያከብራሉ። ይህ በፋኖ ዘንድ የተለመደ አሰራር Read more
በወጣት የሴት አርበኞቻችን ላይ የአብይ አህመድ ሰራዊት የፈጸመውን አረመኔያዊ የጭካኔ ወንጀል አጥብቀን እንኮንናለን፣ እናወግዛለን!
በወጣት የሴት አርበኞቻችን ላይ የአብይ አህመድ ሰራዊት የፈጸመውን አረመኔያዊ የጭካኔ ወንጀል አጥብቀን እንኮንናለን፣ እናወግዛለን የአማራው ሕዝብ በኢትዮጵያ በየትኛውም ሥፈራ በሰላም እንዳይኖር በወያኔና በብልጽግና አገዛዝ ተወስኖ፣ እጅግ ሰቃይና መከራ የተሞላበት ህይወት ሲገፋ ቢቆይም አሁን ደግሞ ከምድረ ገጽ በተለያዩ ስልታዊ መንገዶች ለማጥፋት፣ ባህሉን፣ ቁንቋውን በመለወጥ የስቃይ ዘመኑ ሲበዛበት፣ ህልውናውን ለማስከበር የሞት ሽረት የህልውና ትግል ከጀመረ ሁለት አመታት በላይ አልፎታል። ይህም አልበቃ Read more
“ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት” መፈጠር አስመልክቶ የተሰጠ የድጋፍ መግለጫ
September 25, 2025 ከኢትዮጵያውያን ትብብር ንቅናቄ የተሰጠ የድጋፍ መልዕክት ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት – ቅንጅት በሚል የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ)፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ)፣ እናት ፓርቲ፣ አንድ ኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ (አኢዴፓ) እና የአማራ ግዮናው ንቅናቄ (አግን) ቅንጅት በመፍጠራችሁ ከልብ የመነጨ ደስታችንን እንገልፃለን። ይህ ውሳኔያችሁ፣ የሕዝባችንን የጋራ እሴቶች ንቆ፣ በአግላይ አንቀፆች የተሞላ ሕገ መንግሥት ነድፎ፣ ሀገራችንን በቋንቋ መስፈርት ብቻ Read more
በኢትዮጵያ የፖለቲካ/የሕሊና እሥረኞች የሚያካሄዱት/ያካሄዱት የረሃብ አድማ፣
መስከረም 10፣ 2018 (September 20, 2025 ) አስቸኳይ ጋዜጣዊ መግለጫ ከኢትዮጵያውያን ትብብር ንቅናቄ፣ ጉዳዩ፦ በኢትዮጵያ የፖለቲካ/የሕሊና እሥረኞች የሚያካሄዱት/ያካሄዱት የረሃብ አድማ፣ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ተቃዋሚ ድርጅቶች፣ መሪዎችና አባሎቻቸው፣ የፖለቲካና የሰብዓዊ መብት ተሟዋጓቾች፣ ጋዜጠኞችና ሌሎችም የተለያዩ ሃሳብ አስተናጋጆች፣ በጠ/ሚኒስትር ዓቢይ መንግሥት እየታደኑ፣ በየእሥር ቤቶች መታጏራቸው፣ የተለመደ የዘወትር ሕይወት ለመሆኑ በሀገር ውስጥም፣ በዓለም አቀፉ ደረጃም የታወቀ ሀቅ ነው። Read more
Joint Statement of Ethiopian American Diaspora Organizations and AEPAC on the Ethiopian Government’s Dialogue Commission
FOR IMMEDIATE RELEASE Joint Statement of Ethiopian American Diaspora Organizations and AEPAC on the Ethiopian Government’s Dialogue Commission Philadelphia, PA – August 27, 2025 – A coalition of Ethiopian American diaspora organizations, in partnership with the American Ethiopian Public Affairs Committee (AEPAC), today issued a joint statement rejecting the legitimacy of the Ethiopian government’s Dialogue Commission Read more
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከንቱ ድካም በአሜሪካ
ነሐሴ 23፣ 2017 (August 29, 2025) የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከንቱ ድካም በአሜሪካ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ልዑካን ወደ ሰሜን አሜሪካ ተጉዘው ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን የማነጋገር ከንቱ ልፋት ይመለከታል ይህ መግለጫ። የምክክር ኮሚሽኑ በዐዋጅ ቁጥር 1265/24 ሲቋቋም፣ ራዕዩ “እጅግ መሠረታዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ሀገራዊ መግባባት ተፈጥሮ ማየት” ነው ብሎ ነበር።እሴቶቹን ሲዘረዝር ደግሞ፣ “አካታችና አሳታፊነት፣ገለልተኛነት፣ግልጽነትና Read more
አሳዛኝ የኢትዮጵያኖች እልቂት በኤደን ባሕር ሰላጤ፣
አሳዛኝ የኢትዮጵያኖች እልቂት በኤደን ባሕር ሰላጤ አስቸኳይ ጋዜጣዊ መግለጫ August 7, 2025 የኢትዮጵያውያን ትብብር ንቅናቄ (ኢትን) በኤደን ባሕር ሰላጤ August 3, 2025, በደረሰው የጀልባ መገልበጥ አደጋ በንፁሀን ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ላይ በደረሰው እልቂት የተሰማውን ጥልቅ ኃዘን መግለፅ እንወዳለን። በዚህ አሳዛኝ ሁኔታ 68 ሰዎች መሞታቸው የተረጋገጠ ሲሆን፣ ሌሎች 76 ሰዎች እስከ አሁን በተደረገው አሰሳ ያልተገኙ መሆናቸውን አለም Read more
Another Tragedy in the Gulf of Aden: Ethiopian Lives Lost in the “Route of Death”
FOR IMMEDIATE RELEASE August 7, 2025 Another Tragedy in the Gulf of Aden: Ethiopian Lives Lost in the “Route of Death” Ethiopian Solidarity Movement (ESM) expresses its deepest sorrow and outrage over the tragic shipwreck off the coast of Yemen on August 3, which claimed the lives of at least 76 migrants, many of them Read more
አፍራሽ ይዞታ ያላቸው የባለሥልጣናት ንግግሮች ሊገሩ ይገባል!
በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከመኢአድ፣ ኢሕአፓ፣ እናት ፓርቲ እና ዐማራ ግዮናዊ ንቅናቄ የተሰጠ መግለጫ ከባለሥልጣናት አንደበት የሚወጡ የማይጠበቁ ቃላት አንድ ጊዜ ሲሆን የአፍ ወለምታ ተብሎ ሊወሰድ ይችላል። በተለያዩ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት በተለያዩ ጊዜያት የሚነገሩ ተመሳሳይ ንግግሮች ሥርዓታዊ የአመለካከት አቅጣጫን የሚያመላክቱ መሆናቸው ግን ጥርጥር የለውም። በዚህ ረገድ የሰሜኑ ጦርነት በሚካሄድበት ወቅት የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ሕወሓትና የትግራይ Read more
11ኛው ጠቅላላ ጉባዔን አስመልክቶ ከኢሕአፓ የተሰጠ መግለጫ
ኢሕአፓ ጽናት እስከ ድል በሚል መሪ ሃሳብ ከሃምሌ 14 እስከ ሃምሌ 15 ቀን 2017 ዓ.ም ጠቅላላ ጉባዔውን በሲዳማ ክልል ሃዋሳ ከተማ ሲያካሂድ ቆይቷል፡፡ በዚህ ጉባዔ ላይም ከመላው ኢትዮጵያ የተወጣጡ የኢሕአፓ አባላት ተሳትፈዋል፡፡ በጉባዔው ላይ የኢሕአፓ መስራቾችና የቀድሞ አባላት እና አማካሪዎች የሆኑት መርሻ ዮሴፍ፣ ክፍሉ ታደሠ እና መንግስቱ ሙሴ (ዶ/ር) ከባህር ማዶ ኢሕአፓን እና ወቅታዊ ሁኔታን Read more
የኢትዮጵያ የጤና ባለሞያዎችን ትግል እንደግፋለን!
በመላ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የጤና ባለሙያዎች ለወራት የዘለቀው ሰላማዊ የደመወዝ ክፍያ ጥያቄ ምላሽ ባለማግኘቱ ከፊል ሥራ ማቆም ጀምረዋል። መንግሥት ባለሞያዎቹ ላነሷቸው ጥያቄዎች ምላሽ በመስጠት ማኅበረሰባቸውን እንዲያገለግሉ ለማድረግ ፈቃደኛ ባለመሆኑ ባለሞያዎቹ ግንቦት 17 ቀን 2025 ሥራ የማቆም ውሳኔ ላይ ደርሰዋል። ባለፉት ሁለት ወራት ውስጥ ሐኪሞች፣ ነርሶችና ሌሎች የጤና አጠባበቅ ባለሙያዎች ለጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ፅህፈት ቤት በሰላማዊ መንገድ መደበኛ Read more
የኢትዮጵያውያን ትብብር ንቅናቄ:- የኢትዮጵያ ዶክተሮችና የጤና ሙያተኞች ንቅናቄን ስለመደገፍ፤
ግንቦት 7,2017 ዓ.ም. ለሚመለከተው ሁሉ፣ በአስቸኳይ ይሰራጭ፤ ጉዳዩ፤ የኢትዮጵያ ዶክተሮችና የጤና ሙያተኞች ንቅናቄን ስለመደገፍ፤ የኢትዮጵያ ዶክተሮችና የጤና ባለሙያዎች እያደረጉት ያለው እንቅስቃሴ፣ የሚሰጣቸው ደሞዝ ኢትዮጵያ ዛሬ በምትግኝበት ኢኮኖሚያዊና የኑሮ ሁኔታ በበቂ ሊያኖራቸው የማይችል መሆኑን፣ የጤና መድህን (ኢንሹራንስ) እንደሌላቸውና እንደሚያስፈልጋቸው፣ የሚሠሩባቸው ሁኔታዎችም ምቹ እንዳልሆኑ በመግለጽ ጉዳያቸው በሰላማዊ መንገድ መፍትሄ እንዲሰጠው ለሚመለከተ የመንግስት አካል ከአንድ ወር በፊት ማቅረባቸው Read more
የጤና ባለሙያዎች ድምጽ ይሰማ!!! *ከኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ – ኢሕአፓ የተሰጠ መግለጫ*
*ከኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ – ኢሕአፓ የተሰጠ መግለጫ* የዜጎች ጤና እንዲጠበቅ ሐኪሞች፣ ነርሶች፣ የጤና መኮንኖች፣ ድሬሰሮች፣ የላብቴክኒሽያኖችና ሌሎችም የጤና ባለሙያዎችና ሠራተኞች በልተውና ጠጥተው፣ መጠለያና ሌሎችም ፍላጎቶቻቸው ተሟልተውላቸው ለመኖር መቻል አለባቸው። በጦርነት ኢኮኖሚ እየደቀቀች ባለች ሀገር ዉስጥ ሠላም ከመታጣቱና ፀጥታም በበርካታ የሀገራችን ክፍሎች ከመበላሸቱ በተጨማሪ የኑሮ ውድነቱ እጅግ ከባድ ሆኗል። ዜጎች በተለይም የወር ደሞዝተኞች በሀገራችን ውስጥ Read more
ስምንት ድርጅቶችን ያቀፈ የኢትዮጵያውያን ትብብር ንቅናቄ (ኢትን) ምስረታ ጋዜጣዊ መግለጫ
ጋዜጣዊ መግለጫ ጉዳዩ: – በውጪ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን፣ የሰብዓዊ መብት፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ተሟጋቾችና ታጋዮች የፈጠሩትን ኅብረት ስለማሳወቅ። ሀገራችን ኢትዮጵያ በታሪኳ ደርሶባት የማያውቅ ከፍተኛ ፈታኝ ወቅት ላይ ትገኛለች። እንደ ሀገር የመቀጠል ዕድሏ ፈተና ውስጥ ገብቷል። በአንድነት፣ አብሮ ተስማምቶ ተጋብቶና ተዋልዶ የነበረው ሕዝቧ፣ ባለፉት 34 ዓመታት፣ ሆን ተብሎ በተተከለበት የዘር ፖለቲካ፣ ዛሬ አማራ፣ ትግሬ፣ ኦሮሞ Read more
በወጣቷ ላይ የደረሰው ሰቆቃ በቅርብ ጊዜያት በአገራችን ለተፈጸሙ ግፎች በቂ ማሳያ ነው!
*በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከመኢአድ፣ ኢሕአፓ፣ ዐማራ ግዮናዊ ንቅናቄና እናት ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ* ከምትማርበት ዩኒቨርስቲ ከዓመታት በፊት ከሌሎች ጓደኞቿ ጋር ታፍና ተወስዳ እጅግ አሰቃቂ በደል ከደረሰባቸው አንዷ እንደሆነች የገለጸችው ወጣት ብርትኳን ተመስገን የደረሰባትን ግፍና አኹን እየመራች ያለችውን እጅግ ፈታኝ የሕይወት ውጣ ውረድ የዚህ ዓይነት ጥቃት ሰለባ የሆኑ ሰዎች በማይደፍሩት መልኩ በድፍረት በሚዲያ ቀርባ አስረድታለች። ይኼ በሕዝባችን Read more
አማራ፣ ኦሮሚያ፦ መንግሥት በተስፋፋ ሁኔታ የሚፈጸም የሰዎች እገታን ሊያስቆምና ተጠያቂነትንም ሊያረጋግጥ ይገባል. – ኢሰመኮ
በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች አሳሳቢ ሆኖ የቀጠለውን የእገታ ተግባር ዘላቂ በሆነ መልኩ ለማስቆም ለሰዎች እገታ መነሻና አባባሽ ምክንያት የሆነውን የሰላም መደፍረስና የትጥቅ ግጭትን በዘላቂነት በሰላማዊ መንገድ መፍታትን ጨምሮ ውጤታማ እርምጃዎችን መውሰድ አስፈላጊ ነው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በአማራና በኦሮሚያ ክልሎች ያለውን የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ መከታተሉን የቀጠለ ሲሆን፣ በተለይም እገታን በሚመለከት የቀረቡለትን አቤቱታዎች መነሻ በማድረግ እንዲሁም Read more
የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅትን (የIMFን) ጎጂ ቅድመ ሁኔታዎች ኢትዮጵያ መቀበልዋ የህዝባችንን ኑሮ እጅጉን ይጎዳል
ከኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) በወቅታዊ ጉዳይ ላይ የተሰጠ መግለጫ እያንዳንዱ አገር በአጭርና በረጅም ጊዜ ለማሳካት የሚሻቸው ሦስት – አራት የኤኮኖሚና የልማት ግቦች አሉት። እነዚህም የኤኮኖሚ ዕድገት ማስመዝገብ፣ የሥራ ዕድል መፍጠርና የህዝቡን ህይወት የሚያሻሽሉ ልማቶች እንዳይደናቀፉ “ፊስካል” ና “ሞነታሪ” ፖሊሲዎችን እንዳስፈላጊነታቸው መውሰድ ነው።እነዚህም የባንኮችን የወለድ መጠን ማሳደግ ወይንም መቀነስ፣ ባንኮች መያዝ ያለባቸውን ሪዘርቭ መጨመር ወይንም Read more
ከኢትዮጵያውያን ማሕበር በሆላንድ ጊዜያዊ አመራር የተሰጠ መግለጫ
የኢካን ዓላማ በኔዘርላንድ የሚኖረውን ትውልደ ኢትዮጵያውያንን እና ኢትዮጵያውያንን ኮምዩኒቲይ የማሰባሰብ ሳይሆን የመከፋፋልና የማዳከም ተልኮን ያነገበ ነው። አገር ! ለየአንድ ሠው ቋንቋው፣ ልማዱ፣ ባሕሉ፣ እምነቱ፣ አስተሳሰቡ፣ ወጉና በአጠቃላይ እሱነቱና ማንነቱ የሚከበርበት ብቸኛ ሥፍራ ነው። ኢትዮጵያውያንም በስደት በሚኖሩባቸው አገራት ሁሉ እነኝህን በስደት ያጧቸውን የግልና የጋራ ማንነቶቻቸውን በአንድ ላይ ሆነው ለመዘከር እንዲያስችላቸው በማሰብ የተለያዩ ማዕከላትን በመፍጠር “ኢትዮጵያውያን በሚኖሩበት Read more
ፋሽስቱ ብልጽግና፤ ከእሳቱ ለመውጣት እሾኽ መጨበጥ ትርፉ መጋጋጥ!
የትግል ግንባር በማስፋት የሚዛባ ኃይል፤ የሚቀር ድል የለም! (ከአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ የተሰጠ መግለጫ) ግንቦት 27/2016 ዓ.ም ንጋት ላይ በአማራ ጠቅላይ ግዛት በሰሜን ጎንደር ዞን አድርቃይ ወረዳ፣ አሊጣራ ቀበሌ ‹አንካቶ› በተባለ አካባቢ፣ ሰርገው መንገድ በተከፈተላቸው የትሕነግ ታጣቂዎች በተፈጸመ የጅምላ ጥቃት በርካታ ሰብዓዊና ቁሳዊ ጉዳት ደርሷል፡፡ በቅድሚያ በዚህ አሳዛኝ የጅምላ ጥቃት ለሞቱ ወገኖቻችን ነፍስ Read more
ከአማራ ሕዝባዊ ማሕበራት ፎረም የተሰጠ አስቸኳይ መግለጫ
ሕገ መንገስቱ ሕገ አራዊት ካልሆነ ሕግ ይከበር ! አንድ የሆነን ማሕበረሰብ ወይም አካል አንድ ሁኑ ማለት ይከብዳል፡፡ ምንአልባትም የተሻለ ሊሆን የሚችለው የበለጠ አንድ ሁኑ ማለት ሳይሻል አይቀርም፡፡ በመሰረቱ፣አንድ እንሁን ያልነው አንድ የመሆን ተፈጥሯዊ ማንነታችን ስለሚፈቅድ ነው፡፡ መገለጫችን ስለሆነና ስለምንችል እንዲሁም አንድ መሆን ማለት የግዴታ አንድ አይነት ማለትም አይደለም፡፡ ‹‹ አንድ እንሁን ›› ያልነው አንድ አለመሆናችን Read more
ከኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) የተሰጠ መግለጫ
አገራዊ ምክክር ውጤታማ የሚሆነው አካታች ሲሆንና ሂደቱም ነፃና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ ውሳኔዎቹን ለመተግበር አስቻይ ሁኔታዎች ሲኖሩ ነው! ሀገራችን ኢትዮጵያ ከጊዜ ወደ ጊዜ ከአንድ ቀውስ ወደ ሌላ ቀውስ እየገባች፤ የጋራ እሴቶቻችን፤ ሀገራዊ ራዕያችንና ለዘመናት ሕዝባችን አጋምደው ያኖሩን ትስ ስሮቻችን እየተሽረሽሩ ሄደው ሊጠገኑ ወደማይችሉበት ድረጃ የተደረሰበት ጊዜ ላይ ደርሰናል። በሕገ መንግሥቱ፡ በክልሎች አወቃቀር፡ በሀገር መንግሥት ምሥረታ … ወዘተ Read more
ኢትዮጵያ – ብሔራዊ የአገር ማዳን ጥሪ
ኢትዮጵያ – የአገር አድን ጥሪ ክፍል 1 የ63 ዓመቶች የፖለቲካ ጉዞ – ከ1953-2016 ዓም መግቢያ ይህ ሰነድ የኢትዮጵያ አስከፊና ህልውናዋንም የሚፈታተን መስቀለኛ መንገድ ላይ መቆሟን ይገልፃል። ይህም ሁኔታ የሚያሳየው እንደ ሉዓላዊ አገር የመቀጠል፣ ወይም በቅርቡ እንዳየናቸው አገሮች የመፈራረስ፣ ለአካባቢው አገሮችና ለሰፊው ቀጠና የቀውስ ምንጭ መሆን ነው። ያ እንዳይሆን ውድ ዜጎችዋ በረዥም የታሪክ ሂደት ያካበቱትን እሴቶችና Read more
መንግሥት የሚመራበትን ሕገ መንግሥት ማክበር ግዴታው ነው
የኢሕአፓ ሊቀመንበርና ሌሎችም የኅሊና እስረኞች ያለምንም ቅድመ-ሁኔታ ይፈቱ ግንቦት ፰ ቀን ፪ ሺህ ፲፮ ዓ. ም ኢትዮጵያ እንደ አገር እንድትቀጥል በአገራችን ውስጥ የሕግ የበላይነት ሊኖር ይገባል። የአገር ሕገ-መንግሥት ዜጎች ብቻ ሳይሆኑ መንግሥትም የሚገዛበት የአገሪቷ ሉዓላዊ ሕግ መሆኑ መታወቅ ይኖርበታል፡፡ የመንግሥት ፈርጣማ ጉልበት በሕገ መንግሥት የሚገታ ካልሆነ አንድ መንግሥት ሕዝብን ብቻ እንዳፈተተኝ አስተዳድርበታለሁ ካለ ሕገ መንግሥቱ ቅቡልነት አይኖረውም። የመንግሥት Read more
በተነኮሱን ቁጥር እየተጣመርንና እየጠነከርን እንሄዳለን !!
ሚያዚያ 16፣ 2016 ዓ/ም ትህነግ በወልቃይት ጠገዴ፣ ጠለምትና ራየ አማራ ላይ የፈጸመዉ ግፍና መከራ ያንገሽገሸው ማህበረ ሰብ ራሱን ነፃ ለማውጣትና ህልውናዉን ለማስከበር ባደረገው እልህ አስጨራሽ ትግል አይቀጡ ቅጣት ቀጥቶና አዋርዶ ወደመጣበት እንዲመለስ ከአደረገ በኋላ ላለፉት ሦስት ዓመታት ቀጠናዉን ሰላም በማስፈን ነፃነቱን ሲያጣጥም ቆይቷል። ጦርነትን እንደቋሚ መርህ የሚመለከተውንና ካለጦርነት እስትንፋስ የማይኖረዉን በጥቂት ግለሰቦች የሚዘውር ድርጅት ዕድሜና Read more
በህወሓት የተቀሰቀሰው ጦርነት በአስቸኳይ ይቁም!
ከኢሕአፓ የድጋፍ አስተባባሪ ኮሚቴ የተሰጠ መግለጫ የብልጽግና አገዛዝና ህወሓት በትግራይ፤ በአማራና በአፋር ክልሎች በሚሊዮን የሚገመተውን የወገኖቻችንን ነፍስ የቀጠፈውንና ሚሊዮኖችን ከቀያቸው ያፈናቀለውን ጦርነት ለሁለት ዓመታት ካካሄዱ በኋላ ዳግም ሌላ ጦርነትን ያደርጋሉ ተብሎ አይታሰብም ነበር፡፡ ሕዝባችን በታሪኩ አይቶት የማያውቀው ረሃብና ድህነት እያሰቃየው ባለበት በአሁኑ ወቅት ለሌላ ጦርነት መነሳታቸው እጅግ አሳዛኝ ክስተት ነው። የትግራይና የአማራ ሕዝብ ጦርነት ባስከተለው Read more

























