ኦነግ
News

የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል

ኦነግ አወዛጋቢ ማንነቱና ያልረጋ የፖለቲካ ሩጫው ዛሬም መነጋገሪያ ሆኗል። ቀደም ሲል ለኦሮሞ ትግል እንደ አንድ ብቸኛና ልዩ ምልክት ተደርጎ የተወሰደው ኦነግ በአራት ጎራ ተከፍሎ ቢቆይም አገር ቤት ከገባ በኋላ አንድ መሆን አልቻለም።

በኤርትራ በረሃ እያለ እርስበርስ ጎራ ለይቶ በጥይት የተጫረሰው ኦነግ፣ በአውሮፓና በአሜሪካ ባሉ የተለያዩ አመራሮቹ የስልጣን ሽኩቻ አንድ መሆን አቅቶት ሁለት ዐሥርተ ዓመታት አስቆጥሮ አሁን አገሪቱ ውስጥ በተፈጠረው የፖለቲካ ለውጥ ሁሉም አካላት ወደ አገር ቤት ቢገቡም ልዩነታቸውን ማስወገድ አልቻሉም።

ዳውድ ኢብሣ (ፍሬው ማሾ)፣ አባ ነጋ፣ ገላሳ ዲልቦና ጄኔራል ከማል ገልቹ የተቀራመቱት ኦነግ አራት መልክ ይዞ ወደ አገር ቤት ሲገባ ሕዝብ ጥያቄ ያነሳው “ለምን አንድ አትሆኑም? አንድ ሁኑና ኑ” የሚል ነበር። እነዚህ አራት ክንፎች እንኳን አንድ ሊሆኑ ይባስ ብሎ አቶ ዳውድ ኢብሣ የሚመሩት ኦነግ ሸኔ በሚል ሁለት መልክ ይዞ መጣ።

የፕሮፌሰር መረራ ፓርቲ ኦፌኮ ከአቶ ዳውዱ ኦነግ ሸኔና ከጄኔራል ከማል ገልቹ ሽራፊ ኦነግ ጋር ግንባር ለመፍጠር መስማማታቸው ይፋ ቢሆንም፣ አቶ ዳውድ መቀሌ የመሸገው ህወሓት ካደራጀው የፌደራሊስቶች ኃይል ጋር ፍቅር መጀመሩ በርካቶችን ጉድ ያሰኘና ህወሓት ክፉኛ በደል ሲፈጽምባቸው በነበሩ የኦሮሞ ልጆችና ቤተሰቦች እንዲሁም ባጠቃላይ የኦሮሞ ማኅበረሰብ ዘንድ “አይ ዳውድና ድርጅቱ!?” በሚል ሙሾና ሽሙጥ እየተሰነዘረበት ነው።

ኦነግ ሸኔ – መንታ ትግል

ዳውድ ኢብሣ የሚመሩት ኦነግ ሸኔ አንድም ቁራሽ መሬት በቁጥጥሩ ሳያውል ከኤርትራ የበረሃ ኑሮ ወደ ኢትዮጵያ ሲገባ ወታደሮቹ ደግሞ በትግራይ በኩል ሲገቡ እነ ስብሃት ነጋ በቀይ ወጥ ግብዣ አድርገውላቸው ነበር። ኦነግ ሸኔ ወደ ትግራይ በረሃ ያሽቀነጠራቸውን ኃይል ለእንኳን ደህና መጣህና ለቀይ ወጥ ግብዣ ሲመርጡ ነበር ወዲያውኑ “የማይረጥቡ አሣዎች” የሚል ስያሜ የተሰጣቸው። “አይቼሽ ነው ባይኔ ወይስ በቴሌቪዥን” ሲሉ የዘፈኑላቸውም ጥቂት አልነበሩም።

ሥጋቱ ብዙም ሳይቆይ አቶ ዳውድ “ይቅርታ ሰጪም፣ ይቅርታ ተቀባይም የለም” ሲሉ የፍየል ከመድረሷ ቅጠል መቅንጠሷ ፖለቲካቸውን ጀመሩ። ቄሮ ትግሉን ባፋፋመበት ወቅት “የቄሮ አደረጃጀት ባለቤት ማንም ሳይሆን እኛ ነን” ሲሉ ከኤርትራ የጫጉላ ሰፈራቸው በወረዛ የቪዲዮ መልዕክት ያስተላለፉት አቶ ዳውድ በወቅቱ ጃዋርን “አትንተክተክ” ሲሉትም ተደምጠው ነበር።

በኦነግ ምስኪን ወታደሮች ላይ የተፈጸመው የእርስ በእርስ መገዳደልና በአመራር ውሳኔ ህይወታቸውን ያጡ፣ የተሰቃዩ፣ በእስር ማቅቀው ያለፉት ጉዳይ ራሱን የቻለ አጣሪ እንደሚያስፈልገው የዳውድ ኢብሣ ኮቴ አዲስ አበባ ሲረግጥ መወትወት የጀመሩ ቢኖሩም አዋራው የፈጠረው ጩኸት ሰሚ እንዲያገኙ አላስቻላቸውም። በተመረዘ ምግብ በአንድ አዳር ዳውድ ሲተርፉ የተቀሩት እምሽክ ያሉበት ግፍና የኦነግ ሠራዊት ኤርትራ በረሃ የደረሰበት አስነዋሪ ግፍ ፋይል ግን አልተዘጋም። ቀኑን ጠብቆ ይከፈታል የሚል እምነት በበርካቶች ዘንድ አለ።

ሙሉውን ለማንበብ

ምንጭ፡http://www.goolgule.com/

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *